| |
|
በተጠናከረና በተቀናጀ የመንገድ ጥገናና የትራፍክ ደህንነት የአገራችን የኢኮኖሚ እድገት ይረጋገጣል!
መንገድ በአንድ አገር ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ ጉልህ ሚና ከሚጫወቱት መሰረተ ልማቶች አንደኛውና ዋነኛው ነው፡፡ አገራችንም በፍጥነት ከድህነት ተላቃ መከከለኛ ገቢ ካላቸው አገሮች ተርታ ለመቀላቀል እንድትችል፣ አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ የኢኮኖሚያችን የጀርባ አጥንት የሆነውን የግብርና ምርታችን በፍጥነት ወደ ገበያ ለማቅረብ፣ ለታዳጊው ኢንዱስትሪያችን ጥሬ ዕቃነት የሚውሉትን ምርቶች በፍጥነት ወደሚፈለገው ቦታ ለማድረስ፣ እንዲሁም ለግብርናው ግብዓት የሚሆኑትን የኢንዱስትሪ ውጤቶች ለአርሶአደሩ ለማቅረብ በአጠቃላይ ልማታችንን ለማፋጠን በሚደረጉት እንቅስቃሴዎች ውስጥ መንገድ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡
|
|
የኔፓል የልዑካን ቡድን የሥራ ጉብኝት አደረገ
በኔፓል የአካባቢ ልማት ምክትል ሚኒስትር የተመራ የልዑካን ቡድን ከታህሣሥ 6 እስከ ታኀሣሥ 12 ቀን 2002 ዓ.ም. ለሰባት ቀናት በፌደራላዊ አወቃቀር፣ በከተሞች ድህነት ቅነሳና መልካም አስተዳደር ዙሪያ በአዲስ አባባ ፣አዳማ፣ አዋሳ እና ይረጋለም ከተሞች በመዘዋወር የልምድ ልውውጥና የመስከ ጉብኝት አደረገ፡፡
|
|
ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ሽግግር ባስመዘገበችው የላቀ አፈፃፀም የ2ዐዐ9 ብቸኛ ተሸላሚ ሆነች
ኢትዮጵያ በቴክኖሎጂ ሽግግር ረገድ የአግሮስቶን ቴክኖሎጂን ወደ አገር ውስጥ በማስገባትና በማስተዋወቅ ብሎም በአጭር ጊዜ ውስጥ ቴክኖሎጂውን በማስፋፋት በወሰደችው ግምባር-ቀደም እርምጃና ባስመዘገበችውም ከፍተኛ ውጤት የደቡብ-ደቡብ ዓለምአቀፍ የሀብትና የቴክኖሎጂ ልውውጥ ማዕከል /South-South Global Assets & Technology Exchange (SS-GATE)/ የተባለ አለምአቀፍ ድርጅት እ.ኤ.አ ከሰኘቴምበር 3-4 ቀን 2009 ዓ.ም. በቻይና ሻንጋይ ከተማ ባካሔደው ኮንፈረንስ በቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የመኖሪያ አካባቢ በማሻሻልና በሥራ ዕድል ፈጠራ የ2009 ብቸኛ ተሻላሚ አድርጓታል፡፡
|
|
በመከላከያ ሠራዊታችን የተሳካ ተልዕኮ ኮርተናል!
ከሁለት ዓመታት በፊት የሶማሊያ አሸባሪ ኃይሎችና ተባባሪያቸው በአገራችን ያለውን ሰላምና የልማት እንቅስቃሴ ለማደናቀፍ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በጀመሩበት ወቅት ይህንን የፀረ-ሰላምና ፀረ-ልማት ተልዕኮ በማክሸፍ የኢትዮጵያን ደህንነትና ጥቅም የማረጋገጥ ኃላፊነት የተሰጠው ለመከላከያ ሠራዊታችን እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡
|
|
የከተማ ልማትና መልካም አስተዳደር ፕሮግራሞች
የሥራና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ከክልሎች ጋር በቋሚነት በየሶስት ወሩ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የምርጥ ተሞክሮ ልውውጥ ያደርጋል፡፡ በዕቅድ አፈጻጸም ላይ ባጋጠሙ ችግሮች ዙሪያም በስፋት ይወያያል፡፡ ለችግሮቹም በጋራ የመፍትሔ ሐሳቦችንም ያስቀምጣል፡፡
|
|
መንግሥት የመጠለያ ችግሮችን ለመፍታት የጀመራቸውን ፕሮግራሞች አጠናክሮ ይቀጥላል
የዓለም የመጠለያ ቀን በዓመቱ እ.ኤ.አ. በኦክቶበር የመጀመሪያው ሰኞ እንዲከበር የተባበሩት መንግሥታት በወሰነው መሰረት ዕለቱ በዚህ ዓመት ሕብራዊ ከተሞች /harmonious cities/ በሚል መልዕክት በየአገሩ ይከበራል፡፡ መልዕክቱ በተባበሩት መንግሥታት የተመረጠበት ዋነኛው ምክንያት በከተማ ልማቱ ዘርፍ በኢኮኖሚው፣ በአካባቢ ጥበቃ፣ በማህበራዊ አኗኗር ወዘተ የነዋሪዎች ሕብር አስፈላጊነትን ለሁሉም ለማስገንዘብ ነው፡፡
|